ጾም ታድናለች

ነቢዩ ዳንኤል በጾም ስላመነ
ከአንበሶች ጉድጓድ ሕይወቱን አዳነ
ኤልያስ የወጣ በእሳት ሠረገላ
በጾም በጸሎት ነው አይደለም በሌላ
የነፍስንም ቁስል ጾም ድናለች
የሥጋን ፍላጎት እያደከመች
እስቲ ልብ እናድርግ እናስተውል ደግሞ
ጌ ለሐዋርያት ያላቸውን ቀድሞ
ይህ ርኩስ መንፈስ ሊወጣ የሚችል
በጾም በጸሎት ነው እንደ ወንጌሉ ቃል
← መዝሙር