ወደ ማደርያው ገብቼ

ወደ ማደርያው ገብቼ ልስገድ ለእግዚአብሔር
ምሥጋናንም ላናቅርብ ስለ ስሙ ክብር
አዝ
አድርጎልኛልና አመሰግነዋለሁ
በቤተ መቅደሱ እሰግድለታለሁ
ከፊቱ ለመቆም ማልጄ እነሣለሁ
አዝ
በመከራየ ቀን ሆኖኛል መከታ
ቤቱ ተገኝቼ በፍጹም ደስታ
የከንፈሬን ፍሬ ልሰዋ በልልታ
አዝ
ዓሥር አውታር ባለው በበገና
በመላእክቱ ፊት ለማቅረብ ምሥጋና
የአፌንም ነገር ሰምተህኛልና
አዝ
ለስሙ ልምበርከክ ለርሱ እንደ ሚገባ
ስዕለቴን ልፈጽም ላቅርብለት መባ
ወደ አደባባዩ በምሥጋና ልግባ
አዝ
አሸበሽባለሁ ድምጼን አሰምቼ
በቤተ መቅደሱ ሌሊት ተገኝቼ
እንደ ካህናቱ አጆቼን ዘርግቼ
← መዝሙር