ወደአንተ እሰግዳለሁ

ወደአንተ እሰግዳለሁ ሳለሁ በሕይወቴ
ለአንተም እገዛለሁ እስከ እለተ ሞቴ
አንተ ነህና መድኃኒቴ የዘላለም ቤቴ
የነፍስ የሥጋዬ የሕይወቴ ቤዛ
አትበለኝ ችላ በደሌ ቢበዛ
አንተን አምኜ እኖራለሁ ወዴት እደርሳለሁ
አንተን አምኜ እኖራለሁ በአንተም እመካለሁ
ሳይመሽብኝ ቀኑ ሳይጨልም ድንገት
በጽድቅ ጎዳና ልጓዝ ወደፊት
ምራኝ መንገዱን አሳየኝ እንዳልሳሳት
← መዝሙር