የአብ ቃል አክብሮሽ
✦
የአብ ቃል አክብሮሽ እናት ያደረገሽ
እግዚአብሔር በቃለ ፍጹም ያከበረሽ
የምንመካብሽ መሰላል አንቺ ነሽ ፪
እግዚአብሔር በቃለ ፍጹም ያከበረሽ
የምንመካብሽ መሰላል አንቺ ነሽ ፪
ቅድስና ላንቺ ጽድቅም ላንቺ ሆኖ
ዓለምን የፈጠረ በአንቺ ተወስኖ
የገነት ፍሬ ነሽ ሕይወትን ያፈራሽ
አንቺን ለመረጠ አንቺን ላነጻሽ
ምስጋና ይድረሰዉ ለቸሩ አምላክሽ ፪
ዓለምን የፈጠረ በአንቺ ተወስኖ
የገነት ፍሬ ነሽ ሕይወትን ያፈራሽ
አንቺን ለመረጠ አንቺን ላነጻሽ
ምስጋና ይድረሰዉ ለቸሩ አምላክሽ ፪
አዳም የኖረብሽ የኤዶም ገነት ነሽ
የኤፌሶን ወንዝ ወርቅ የሚፈልቅብሽ
የግዮን ማዕበል ኢትዮጵያን የከበብሽ
ዮርዳኖስን ሆነሽ አሕዛብን ፈወስሽ
በልጁ ቃልነት አብም አከበረሽ ፪
የኤፌሶን ወንዝ ወርቅ የሚፈልቅብሽ
የግዮን ማዕበል ኢትዮጵያን የከበብሽ
ዮርዳኖስን ሆነሽ አሕዛብን ፈወስሽ
በልጁ ቃልነት አብም አከበረሽ ፪
መዓዛሽን ወዶ ወልድ ዋሕድ ዋጅሽ
አብም በሰማያት በኅሊናዉ ሳፈሽ
መንፈስቅዱስ መጥቶ አንቺን አከበረሽ
እመካብሻለሁ እመቤቴ ስልሽ ፪
አብም በሰማያት በኅሊናዉ ሳፈሽ
መንፈስቅዱስ መጥቶ አንቺን አከበረሽ
እመካብሻለሁ እመቤቴ ስልሽ ፪
ወልድ በመዉደዱ ከአንቺ መወለዱን
ንጹሕ ሆኖ አግኝቶት ቅዱሱ ሥጋሽን
ለቃሉ ማደሪያዉ ጽላትና ታቦት
በብሩህ ደመና ተመስለሽለት
ከሥጋሽ ተከፍሎ ከደምሽ ደም ወስዶ
ከነፍስሽም ነፍስ ፍጹም ተዋሕዶ ፬
ንጹሕ ሆኖ አግኝቶት ቅዱሱ ሥጋሽን
ለቃሉ ማደሪያዉ ጽላትና ታቦት
በብሩህ ደመና ተመስለሽለት
ከሥጋሽ ተከፍሎ ከደምሽ ደም ወስዶ
ከነፍስሽም ነፍስ ፍጹም ተዋሕዶ ፬
✦