የአብርሃም አምላክ

የአብርሃም አምላክ የይስሐቅም ቤዛ
ወገኖቹን ሁሉ በራሱ ደም ገዛ
የሐሰት ምስክር አቁመው ከሰሱት
በሞት እንዲቀጣ ሁሉም ፈረዱበት
ጲላጦስ ገረፈው በሰንሰለት አስሮ
በአይሁድ መካከል እንዲኖር ተከብሮ
ድንግል አልቻለችም ዕንባዋን ልትገታ
እያየች በመስቀል ልጇ ሲንገላታ
በብርሃን ዙፋን ላይ የቆሙት እግሮቹ
በችካር ላይ ቆሙ ምንም አልሰለቹ
የብርሃን አክሊልን ለሰማዕት ያደለ
የሾህ አክል ደፍቶ ቀራንዮ ዋለ
ዘማሪ መዝሙረ ስብሐት
← መዝሙር