የሕያዋን አምላክ

በእኩለ ሌሊት ክርስቶስ ተነሣ
ሙታን ይደለንም ክርስቶስ ተነሣ
ሕያዋን ነን እኛ ክርስቶስ ተነሣ
በመስቀሉ የዳንን ››
ከኃጢአት ቁራኛ ››
የተዋረደውን ››
ሊያከብር ዳግመኛ ››
ሞትን አሽንፎ ››
ተነሣልን ለእኛ ››
አዝ ---
እናንተስ አትፍሩ ክርስቶስ ተነሣ
እነግራችኋላው ››
የተሠቀለውን ››
እንድትሽ አውቃለው ››
ሕያዉን ከሙታን ››
ለምን ፈለጋችሁ ››
እንደተናገረው ››
ተነሥቷል ጌታችሁ ››
አዝ ---
ክርስቶስ ሲነሣ ከርስቶስ ተነሣ
በሰንበት ሌሊት ››
አስቀድሞ ታየ ››
ለመግደላዊት ››
እርሷም ትንሣኤውን ››
ለዓለም አበሠረች ››
ጌታዬን አየሁት ››
ተንስቶአል እያለች ››
አዝ ---
← መዝሙር