የሕይወቴ መታመኛ

የሕይወቴ መታመኛ የነፍሴ ተስፋ ጌታዬ አምላኬ
መድኃኔዓለም ላመስግንህ እጠግባለሁ በውዳሴህ
መላእክት በሰማያት ቅዱስ አንተ ነህ እያሉ
በክንፋቸው አሸብሽበው
ይጠሩሃል በዝማሬያቸው
ቅዱስ ዳዊት በበገና ከእሥራል ሀገር
በተመስጦ ወደ አርያም ዘልቆ
ዘመረልህ አንተነትህን አውቆ
ሕፃናትም አንተን አምነው
በአህያ ተቀምጠህ ስትመጣ
አፍ አውጥተው አመሰገኑ
ሆሣዕና በአርያም አሉ
ሃሌ አለ ቅዱስ ዳዊት
ጸናጽል መቋሚያ አንሥቶ
ምስጋናህን በልቡ ሽቶ
በመንፈስህ በአንተ ተመርቶ
ፈለጉንም ተከትለው
ካህናት በሙሉ ቆመው
ይቀኛሉ ለቅዱስ ስምህ
በማኅሌት በመመስገኛህ
እስትንፋስም ያለው ሁሉ
ያመስግንህ አንተን በእውነት
ከልብ ሆኖ በንጹሕ እምነት
እንደ ዕዝራ እንደ ዳዊት
← መዝሙር