የቅዱሳን አምላክ
✦
አብርሃምን ከካራን የጠራኸዉ ጌታ
ለሙሴ በሲና የሆንከዉ መከታ
ልጠፋ ነዉና በሥጋ ፍላጎት
የይስሐቅም ጌታ ሕይወቴን ታደጋት ፪
የኤርትራን ባሕር በኃይልህ የከፈልክ
በሲና በረሃ ሕዝብህን የመገብክ
ኖኅ ከጥፋት ዉኃ የዳነብህ አምላክ
ሎጥን እንዳዳንከዉ ፍጹም ምሕረትን ላክ ፪
የተነበዮልህ ነቢያት በሙሉ
አምላክ ሰዉ ይሆናል ይወለዳል ሲሉ
ከዓሣ አንበሪ ሆድ ዮናስን ያወጣህ
ዓለም ልትዉጠኝ ነው አይለየኝ ጸጋህ ፪
ሥጋን ተዋሕደህ በወሰንከዉ ሰዓት
የሞትክልኝ አምላክ ያዳንከኝ ከሞት ሞት
እንደወንጌልህ ሕግ የምኖር አድርገኝ
በመጨረሻዉ ቀን በቀኝህ አድርገኝ ፪
አልቻልኩኝምና ልፈጽም ሕግህን
የሐዋርያት አጽናኝ ስጠኝ ብርታትህን
ምግባረ ጎደሎ ሆኛለሁኝና
የቅዱሳን አምላክ እርዳኝ እንድጸና ፪
ለሙሴ በሲና የሆንከዉ መከታ
ልጠፋ ነዉና በሥጋ ፍላጎት
የይስሐቅም ጌታ ሕይወቴን ታደጋት ፪
የኤርትራን ባሕር በኃይልህ የከፈልክ
በሲና በረሃ ሕዝብህን የመገብክ
ኖኅ ከጥፋት ዉኃ የዳነብህ አምላክ
ሎጥን እንዳዳንከዉ ፍጹም ምሕረትን ላክ ፪
የተነበዮልህ ነቢያት በሙሉ
አምላክ ሰዉ ይሆናል ይወለዳል ሲሉ
ከዓሣ አንበሪ ሆድ ዮናስን ያወጣህ
ዓለም ልትዉጠኝ ነው አይለየኝ ጸጋህ ፪
ሥጋን ተዋሕደህ በወሰንከዉ ሰዓት
የሞትክልኝ አምላክ ያዳንከኝ ከሞት ሞት
እንደወንጌልህ ሕግ የምኖር አድርገኝ
በመጨረሻዉ ቀን በቀኝህ አድርገኝ ፪
አልቻልኩኝምና ልፈጽም ሕግህን
የሐዋርያት አጽናኝ ስጠኝ ብርታትህን
ምግባረ ጎደሎ ሆኛለሁኝና
የቅዱሳን አምላክ እርዳኝ እንድጸና ፪
✦