የሰው ልጅ ሁል ጊዜ

የሰዉ ልጅ ሁል ጊዜ በጣም ደስ ቢለዉ
ደግሞ የጭንቁን ቀን ማሰብ ተገቢ ነዉ
ምንም ቢደሰቱ ቢበዛ ምቾች
ድኻም ሆነ ሀብታም እኩል ነዉ በሞት
ሰዉ ሆይ አትጨነቅ ለዓለም ጐዳና
ዓለሙም ንብረቱም ኃላፊ ነዉና
ሀብት አገኘሁ ብለህ በጣም ደስ አይበልህ
ድኸየሁም ብለህ አይዘን ልቦናህ
ይፈራረቃለº አይኖሩም አብረዉህ
%ረ ሰዉ ሆይ ልብህ ለምን ችላ አለ
ከባድ የሞት እዳ በራስህ እያለ
ያ የጨለማ ቀን ትዝ ትዝ እያለኝ
እንባዬ ከመዉረድ አላቆምም አለኝ
← መዝሙር