የሾህ አክሊል

የሾህ አክሊል ጉንጉን ደፍተው በራሱ ላይ
ብለው ዘበቱበት የአይሁድ ንጉሥ ሆይ
በጉልበታቸውም ተንበርከኩና
ሰላም ለአንተ ይሁን አሉት አፌዙና
ራሳቸውንም እየነቀነቁ
መንገደኞች ሁሉ በጌታ ላይ ሳቁ
አወይ ሌለውን ሰው ያድን የነበረው
ምነዋ ራሱን ሳያድን የቀረው
እያሉ ሲነቅፉት በእርሱ ያላመኑ
ምልክት ከሰማይ ታየ ወዲያዉኑ
ፀሐይም ጨለመ ደም ሆነች ጨረቃ
ከዋክብት ረገፉ ዓለት ሁሉ ነቃ
የመቅደሱ ግርዶሽ ከሁለት ሲቀደድ
የሞቱት ተነሡ ከመቃብር ጉድጓድ
← መዝሙር