የትንሣኤ ብርሃን የሰው ልጅ ሕይወት

የትንሣኤ ብርሃን የሰው ልጅ ሕይወት
አዳምን መለሰው ከወጣበት ቤት
እሰይ የምስራች ደስ ይበላችሁ
ሞትን ድል አድርጎ ተነሣላችሁ
ያ በሙሴ ኦሪት የተነገው
ሞትን ዛሬ አጠፍቶ የተነሣው ነው።
…….....አዝ...
ማርያም መግደላዊት ምንኛ ታደልሽ
ከሰው ሁሉ በፊት ትንሣኤን አየሽ
…….....አዝ...
ብርሃን ያሳየዋል የጽድቅንም ፋና
ለሚገዛለቱ በውነቱ ጎዳና
……....አዝ..
ስምህን ተናገርኩ ሁሉም ተቀበለ
ከጥፋት ልጅ በቀር ማንም አልታጎለ
………...አዝ...
አባት ሆይ በጽድቅህ ባርከህ ቀድሳቸው
ከጥፋት ልጅ በቀር ሁሉም ያንተው ናቸው
………....አዝ...
አንድ ይሁኑ እነርሱ በሰላም በፍቅር
እኔም አንድ እንደሆኩ ከአንተ ካባቴ ጋር
← መዝሙር