የወርቅ መሰላል ነሽ

ድንግል ማርያም የወርቅ መሰላል ነሽ
መሰላል ነሽ የወርቅ መሰላል ነሽ
ሰውና አምላክን ያገናኘሽ
አባ ችን ያዕቆብ በፍኖተ ሎዛ
አሸልቦት እንቅልፍ ተኝቶ ከጠ?ዛ
ከምድር እስከ ሰማይ የምትደርስ መሰላል
ምሳሌሽን አየን ማርያም ድንግል
አዝ . . .
መላእክት ሲወጡ ሲወርዱ ከሰማይ
እንደ ያዕቆብ ተኝቶ መንገድ ላይ
ተስፋ አድርጎ ሲኖር የሰላሙን ዘመን
ይኸው ተፈጸመ በአንቺ በእና ችን
አዝ . . .
በአንቺና በልጅሽ ሆነልን ሰላም
በአንቺ ተፈጸመ የያዕቆብ ሕልም
ሰውና መላዕክት ተለያይተው ሲኖሩ
በልጅሽ መወለድ በአንድ ላይ ዘመሩ
አዝ . . .
← መዝሙር