ይለመነናል

ይለመነናል አምላክ አብርሐም
ይታደገናል መድሃኔዓለም
ለፍጥረት ሁሉ እጁን የዘረጋ
ቸር እረኛ ነው አልፋና ኦሜጋ
አብርሐም ይሰሐቅን ያዕቆብን አስበህ
የማልክላቸውን ቃለኪዳን አስታውሰህ
ደካማ ለሆነው ሥጋ ስልጥኖብን
አትመለስ ጌታ የምህረት ዓይንህን
ከሰማየ ሰማይ ይድረስ ጩኸታችን
እንዘን እናልቅስ ስለ በደላችን
ይለመነናል አምላክ አብርሐም
ይታደገናል መድሃኔዓለም
ለፍጥረት ሁሉ እጁን የዘረጋ
ቸር እረኛ ነው አልፋና ኦሜጋ
ባይመለከተን አምላከ አብርሐም
በምሕረት ዓይኖቹ መድሃኔዓለም
ባይዘረጋልን አምላከ አብርሐም
የፍቅር እጆቹን መድኃኔዓለም
ሕዝበ እሰራኤል ሁሉ ለአምላክ ዘምሩ
አደኖናልና በሚያስደንቅ ፍቅሩ
ይለመነናል አምላክ አብርሐም
ይታደገናል መድሃኔዓለም
ለፍጥረት ሁሉ እጁን የዘረጋ
ቸር እረኛ ነው አልፋና ኦሜጋ
ምንም እንኳን ክህደት ቅጥፈት ቢበረታ
ስለ አብርሐም ብለህ አልተወከንም ጌታ
ለቅዱሳን ያለህ ቃል ኪዳን ሲጸና
ቀስተ ደመናህን አይተነዋልና
የእሰራኤል አምላክ የማታንቀላፋ
በፍቅርህ ታደገን በሞት ሳንጠፋ
ይለመነናል አምላክ አብርሐም
ይታደገናል መድሃኔዓለም
ለፍጥረት ሁሉ እጁን የዘረጋ
ቸር እረኛ ነው አልፋና ኦሜጋ
ቃልዳኑ ግሩም አምላከ አብርሐም
ምሕረቱ የበዛ መድኃኔዓለም
ርስት ጉልታችን አምላከ አብርሐም
የህይወታችን ቤዛ መድኃኔዓለም
ሳይጸየፍ ጌታ ያደፈ ኃጢአቴን
ከማጥ ውስጥ አወጣኝ ታደጋት ሕይወቴን
← መዝሙር