ዝናማትም ዘነሙ
✦
ዝናማትም ዘነሙ ወንዞችም ጎረፉ ፪
የአምላክን ጸጋ እያትረፈረፉ ፪
ሰማያትም ዘመሩ በልዑል ቃሉ ፪
የፍጥረታት ሁሉ መጋቢ አንተ ነህ እያሉ ፪
የአምላክን ጸጋ እያትረፈረፉ ፪
ሰማያትም ዘመሩ በልዑል ቃሉ ፪
የፍጥረታት ሁሉ መጋቢ አንተ ነህ እያሉ ፪
ገበሬውም አረሰ ፈጣሪውን አምኖ ፪
ዘርንም በተነ በምድር ላይ ከጎተራው ዘግኖ ፪
ደመናትም ዓለምን ይዞራሉ ፪
በእግዚአብሔር ትዕዛዝ ዝናምን ሊያድሉ ፪
ዘርንም በተነ በምድር ላይ ከጎተራው ዘግኖ ፪
ደመናትም ዓለምን ይዞራሉ ፪
በእግዚአብሔር ትዕዛዝ ዝናምን ሊያድሉ ፪
በልምላሜ ተዋቡ ዕፅዋት አዝርእቱ ፪
ፍሬን ይሰጡ ዘንድ አብዝተው በጊዜው በወቅቱ ፪
መሬትም ለአራሿ አድርጋ ውለታ ፪
የላቡን የወዙን ከፈለች እንዳዘዘ ጌታ ፪
ፍሬን ይሰጡ ዘንድ አብዝተው በጊዜው በወቅቱ ፪
መሬትም ለአራሿ አድርጋ ውለታ ፪
የላቡን የወዙን ከፈለች እንዳዘዘ ጌታ ፪
ድካሙን ጥረቱን አምላክ ተመልክቶ ፪
አንዷን ፍሬ ሰጠው አብዝቶ አድርጎ መቶ ፪
ዝናምንም ለዘር ልምላሜን ለፍሬ ፪
የሰጠን አምላክ ይመስገን ይክበር በዝማሬ ፬
አንዷን ፍሬ ሰጠው አብዝቶ አድርጎ መቶ ፪
ዝናምንም ለዘር ልምላሜን ለፍሬ ፪
የሰጠን አምላክ ይመስገን ይክበር በዝማሬ ፬
✦